登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያ ተከላ ስራ ተጀመረ

发布:5/7/2026 阅读:1

🔇Unmute

ሐረር፤ ሚያዝያ 28/2018(ኢዜአ)፦ በሐረር የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያ ተከላ ስራ ተጀምሯል።

የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያ ተከላ ስራውን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) አስጀምረውታል።

ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በዚሁ ጊዜ የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል ብለዋል።

በተለይም ትክክለኛ የመረጃ ግብዓት ከመስጠት አኳያ ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አመልክተዋል።

የተከላ ስራው በአጭር ጊዜ እንዲከናወን የክልሉ መንግስት እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

የስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሪክተር በላቸው ፀሐይ፤ ቴክኖሎጂው መረጃን በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት ተደራሽ ለማድረግ የላቀ ፋይዳ አለው ብለዋል።

እንዲሁም 35 ኪሎ ሜትር ራድየስን በመሸፈን ትክክለኛ ልኬት የሚወስድና 24 ሰዓት የሚሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያው የመንገድ ዲዛይን፣ አጠቃላይ የኮንስትራክሽን ስራ ለሚያከናውኑ፣ የመሬት አጠቃቀምን በጥንቃቄ ለመቆጣጠር፣ ለይዞታ መረጋገጫና ለሌሎችም መረጃን መስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል።

የሳተላይት የመገኛ መረጃ መቀበያ ጣቢያ ተከላው በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ መሆኑንም ተናግረዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们