登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በአሪ ዞን በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ51 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ለምቷል

发布:5/6/2026 阅读:2

🔇Unmute

ጂንካ፤ ሚያዚያ 28/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ51 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።


የመምሪያው ኃላፊ ጉራልቅ ይዥማልቅ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በበልግ አዝመራው እየለማ ካለው መሬት ውስጥ ከ3 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ብለዋል።


አርሶ አደሩ ከመደበኛው የሰብል ምርት በተጨማሪ የተሻሻሉ የስንዴ፣ የማሽላ እና የበቆሎ ምርጥ ዘሮችን በኩታገጠም በስፋት በማልማት ለሌሎች አካባቢዎች እያቀረቡ መሆኑንም ገልፀዋል።


ዞኑ የተለያዩ የአየር ፀባዮች ያለው በመሆኑም በተለይ በደጋው አካባቢ ስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ እና አተር እየተመረተ መሆኑንም አስታውቀዋል።


ወይናደጋ እና ቆላማ በሆኑት አካባቢዎች ደግሞ ጤፍ፣ ማሽላ፣ በቆሎ፣ ሩዝ፣ ለውዝ፣ ሰሊጥ፣ ማሾ እና መሰል ሰብሎች በስፋት እየለማ መሆኑንም አመልክተዋል።


በአሁኑ ወቅትም አርሶ አደሩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ ምርታማነቱን እንዲያሻሽል በማሰልጠኛ ማዕከላት ተግባር ተኮር ትምህርት እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።


በዞኑ የባካ ዳውላ አሪ ወረዳ አርሶ አደር ማርቆስ አዲሱ፥ በዘንድሮው የበልግ አዝመራ በቆሎና በአጭር ጊዜ የሚደርሱ የጓሮ አትክልቶችንም በማልማት የገቢ አቅማቸውን ማሳደጋቸውን ነው የሚገልጹት።


ሌላው አርሶ አደር ግርማ ከማይ በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመጣመር በ10 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም ስንዴ እያለሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


ከጥቂት ጊዜ ወዲህ የስንዴ ምርት በኢንዱስትሪውም ሆነ በማሕበሩ በስፋት የሚፈለግ በመሆኑ በዘርፉ መስራታቸው ውጤታማ እያደረጋቸው መምጣቱን ጠቁመዋል።


ከግብርና ባለሙያዎች የሚሰጧቸውን ምክረ ሀሳቦች በመተግበራቸውም ምርትና ምርታማነታቸውን እንዳሳደገላቸው ነው የተናገሩት።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们