登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በሀረሪ ክልል ለቱሪዝም ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት አበረታች ውጤት የታየበት ነው

发布:5/6/2026 阅读:2

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ሚያዝያ 26/2018(ኢዜአ)፦ በሀረሪ ክልል ለቱሪዝም ዘርፉ የተሰጠው ትኩረት አበረታች ውጤት የተመዘገበበት ነው ሲሉ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።

በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር የተመራው የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች የልዑካን ቡድን በሀረር ኢኮ ፓርክ የጅብ ትርኢትን ተመልክተዋል።


ከንቲባው በጉብኝታቸው ላይ እንደተናገሩት በክልሉ መሰል የቱሪዝም መስህቦችን ለማስፋፋት የተደረገው ጥረት አበረታች ውጤት የታየበት ነው።

በክልሉ የተገነባው የጅብ ትርዒት ማሳያ ፓርክም ለቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ያሉት ከንቲባው ይህም የቱሪዝም ዘርፉን በማጎልበት ከተማዋን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል።


የሀረር ከተማን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችም ውጤታማና አበረታች መሆናቸውን እንደተመለከቱ ገልጸዋል።

በጉብኝቱ ላይ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪን ጨምሮ የሀረሪ ክልል እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们