登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

ኢትዮጵያ የቱሪዝም ጸጋዎቿን እንድትጠቀም የግል ዘርፉ የሆቴልና የመዳረሻ ልማት ወሳኝ ነው

发布:5/6/2026 阅读:2

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 26/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ጸጋዎች በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል የግል ዘርፉ በሆቴልና በመዳረሻ ልማት ላይ የሚኖረው ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሕር ዳር ታሪኳን ሳትለቅ ዘመኑን እየዋጀች መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

ቀደም ሲል የከተማዋ ትዝታ በነበረው በታሪካዊው ጣና ሆቴል ሥፍራ ዓለም አቀፍ ደረጃን ያሟላ የፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን (Four Points by Sheraton) ሆቴል የግንባታ ፕሮጀክት በይፋ መጀመሩን አመልክተዋል።


በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የሚገነባው ይህ የሆቴል ፕሮጀክት ከተማዋን የቱሪዝም ሠገነት እንደሚያደርጋት ተናግረዋል።

በርካታ አገልግሎቶችን አሟልቶ በአሥራ ስምንት ወራት ግንባታው የሚጠናቀቀው ይህ ሆቴል፣ የግል ባለ ሀብቱ በሀገሪቱ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ውስጥ ያለውን ሚና በተግባር የሚያሳይ ነው ብለዋል።


ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በተለያዩ ዘርፎች እያመጣ ያለው ለውጥ የሚደነቅ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ይህ የሆቴል ግንባታም ለባሕር ዳር በጸጋ ላይ ጸጋ የሚጨምር መሆኑንም ነው የተናገሩት።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ፕሮጀክቱን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት ለከተማዋና ለሀገሪቱ ሕዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们