登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

የኮሪደር ልማቱ ለቱሪዝምና ኢንቨስትመንት መስፋፋት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል

发布:5/6/2026 阅读:2

🔇Unmute

ባሕር ዳር፤ ሚያዝያ 26/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ለቱሪዝምና ኢንቨስትመንት ዘርፉ መስፋፋት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ገለፀ።

የቢሮው ኃላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኮሪደር ልማቱ የተጎሳቆሉ ከተሞችን በማልማት ውበታቸው እንዲወጣ አድርጓል።

የከተሞችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ ከማነቃቃት ባለፈ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴያቸው እንዲነቃቃ ማስቻሉንም ጠቁመዋል።

ከተሞች ለነዋሪዎች የተመቹ እንዲሆኑ ማድረጉን ገልጸው፤ ለቱሪዝም ዘርፉ ማደግና የከተሞችን የኢንቨስትመንት ፍሰት በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም አንስተዋል።

በያዝነው ዓመት በ106 ሔክታር ላይ የኮሪደር ልማት ለመሥራት መታቀዱን እና እስካሁን በ80 ሔክታሩ ላይ መከናወኑን አረጋግጠዋል።

በዚህ ሥራም የተሽከርካሪና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ 108 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ልማት መከናወኑን አስታውቀዋል።

በተሠራው የኮሪደር ልማት 10 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ 168 ደረጃቸውን የጠበቁ ካፍቴሪያዎች፣ የሕጻናት መዝናኛዎች፣ የአረጋውያን ማረፊያዎችና ሌሎች ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጪ ስፍራዎች መካተታቸውን አብራርተዋል።

ለኮሪደር ልማቱ ከ6 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸው፤ ከዚህ ውስጥ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮኑ ሕብረተሰቡ በገንዘብ፣ በጉልበቱና ቁሳቁስ ተሳትፎ ያደረገበት መሆኑን አስገንዝበዋል።

በኮሪደር ልማቱ ለ112 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አመላክተዋል።

በቀጣይ ልማቱን ወደ ሌሎች ከተሞች የማስፋቱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ያመላከቱት።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们