登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀቶች ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ግብዓት እንሆዲኑ እየሰራ ነው

发布:5/6/2026 阅读:3

🔇Unmute

አምቦ፤ ሚያዝያ 23/ 2018 (ኢዜአ)፦ አምቦ ዩኒቨርሲቲ ሀገር በቀል እውቀቶችን ከሳይንስ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ግብዓት እንዲሆኑ በጥናት እያገዘ መሆኑን አስታወቀ ።

አምቦ ዩኒቨርሲቲ ሀገር በቀል እውቀቶች ለዘላቂ ልማት በሚል መሪ ቃል 11ኛውን ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ እይካሄደ ነው።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባይሳ ለታ (ዶ/ር) በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንገለጹት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ብቁ እና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት በትኩረት እየሰራ ነው።

በተለይም በምርምር ስራዎቹ በማህበረሰቡ ውስጥ የሚታዩ ተጨባጭ ችግሮች እንዲፈቱ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ዩኒቨርሲቲው በጤና፣ በግብርና፣ በባህልና በአስተዳደር ዘርፎች ያሉ ሀገር በቀል እውቀቶችን ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ግብዓት እንዲሆኑ የጥናት ውጤቶችን እያበረከተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

የዛሬው የምርምር ከንፍረንስም የማህበረሰቡን ሀገር በቀል እውቀትን በማጥናት ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር በማስተሳሰር ችግር ፈቺ የሚሆንበትን አቅም ለማጎልበት ያለመ ነው ብለዋል።

በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ሰለሞን ማሾ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በዘንድሮው ኮንፈረንስ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና የምርምር ማዕከላት የተውጣጡ ምሁራንና ተመራማሪዎች ያጠኗቸው በርካታ የጥናት ፅሁፎች ለውይይት እንደሚቀርቡ ገልጸዋል።

የቀረቡት ጥናቶች በዋናነት ሀገር በቀል እውቀቶች ላይ ትኩረት ያደረጉና በተግባር ሲተረጎሙም የህብረተሰቡን የእለት ተእለት ችግር የመፍታት አቅማቸው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮንፈረንሱም እውቀቶቹ ከዘመናዊ ሳይንስ ጋር ተቀናጅተው ጥቅም ላይ የሚውሉበትን ሂደት ለማቀላጠፍና በተመራማሪዎች መካከል የልምድ ልውውጥ እንዲኖር ለማድረግ አቅም እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።

በመድረኩ ላይ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ ተመራማሪዎች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የታደሙ ሲሆን፣ ለሁለት ቀናት በሚቆየው ኮንፈረንስ በተመረጡ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ የጥናት ውጤቶች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው ተመላክቷል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们