登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘው የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪና አስተዳደር ስርዓት ሐሰተኛ መረጃን ለመከላከል ጉልህ ሚና አለው

发布:5/6/2026 阅读:2

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘው የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና የአስተዳደር ስርዓት ሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን ለመከላከልና መቆጣጠር ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ ገለጹ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ጋር በመተባበር ያለማውን የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ስርዓት ቴክኖሎጂ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር በመካሄድ ላይ ነው።


በመርሐ ግብሩ ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ፣ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፣ የመገናኛ ብዙኃን የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

ተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና አስተዳደር ስርዓት ቴክኖሎጂ ወደ ተግባር እንዲገባ መደረጉ የባለስልጣኑን እና የዘርፉን ሥራዎች ዘመናዊ ወደ ሆነ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ቴክኖሎጂው የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው።

የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪ እና የአስተዳደር ስርዓት የመገናኛ ብዙኃን የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓትን እንደሚያዘምን ገልጸው፥ ኢትዮጵያ እየተገበረች ካለው የዲጂታላይዜሽን ሥርዓት ጋር የተጣጣመ ነው ብለዋል።

የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትንና የጥላቻ ንግግርን መከላከልን በሰው ሰራሽ አስተውሎት በመታገዝ ውጤታማ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።

የሚዲያዎችን ሕጋዊነት ለማረጋገጥ እና በዘርፉ ላይ ግልፅ የሆነ የክትትልና ቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፥ ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ለሁሉም በሚል መሪ ሀሳብ እየሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የመገናኛ ብዙኃን አሠራርን በማዘመን ሀገራዊ ሚናውን በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ዛሬ ይፋ የሆነው የሚዲያ ሬጉላቶሪና አስተዳደር ቴክኖሎጂ ለዘርፉ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አመልክተዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们