登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በዐውደ ርዕዩ የቀረቡ የፈጠራ ውጤቶች ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች ማሳያ ናቸው

发布:5/6/2026 阅读:2

🔇Unmute

ድሬደዋ፤ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡-በዐውደ ርዕዩ የቀረቡ የፈጠራ ውጤቶች ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች ማሳያ መሆናቸውንየድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።

"ሳይንስና ቴክኖሎጂ፤ ለፈጣን አገራዊ ዕድገትና ለውጥ" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀውና በድሬዳዋ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተሰሩ የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ውጤቶች ዐውደ ርዕይ በድሬዳዋ ተጀምሯል።


ዐውደ ርዕዩን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ የአስተዳደሩ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር፣ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ እና ሌሎች አመራሮች ከፍተውታል።

ከንቲባ ከድር በወቅቱ እንዳሉት፤ በዐውደ ርዕዩ የቀረቡ የፈጠራ ውጤቶች ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች ማሳያ ናቸው።


በመጀመሪያና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እየተከናወኑ የሚገኙት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገርም አስተዳደሩ ድጋፉን እንደሚያጠናክር ተናግረዋል።

በዐውደ ርዕዩ የቀረቡት የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ በመሆናቸው ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በማስተሳሰር ፈጠራዎቹን ወደ ጥቅም የማሸጋገር ስራ በትኩረት ይከናወናል ብለዋል።

የብልፅግና ጉዞው በፍጥነትና በጥራት የሚሳካው ለቴክኖሎጂ ውጤቶች ልዩ ትኩረት እና ድጋፍ በማድረግ መሆኑንም አንስተዋል።

የአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ በበኩላቸው፤ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በድሬዳዋ በሚገኙ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለቴክኖሎጂ እና ለሳይንስ ፈጠራዎች ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አስረድተዋል።


የአሁኑ የትምህርት ቤቶች የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችም የአሰራርና አደረጃጀቶች እንዲሁም የድጋፍ እና ክትትል ውጤቶች ናቸው ብለዋል።

በትምህርት ቤቶቹ የተሰሩት የቴክኖሎጂ ውጤቶች የተማሪዎችን የፈጠራ አቅም የሚያሳዩ በመሆናቸው ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።

የፈጠራ ስራዎቹም የበለጠ ዳብረው ለአምራች ኢንተርፕራይዞች፣ ለኢንዱስትሪዎች እና ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጥቅም እንዲውሉ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ዛሬ በተከፈተው እና ለሶስት ቀናት በሚቆየው ዐውደ ርዕይ ላይ በመስኖ፣ በኤሌክትሪክ፣ በአገልግሎት፣ በህክምና፣ በመማር ማስተማርና ለሌሎች ዘርፎችም የሚያግዙ የፈጠራ ስራዎች ቀርበዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们