登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የቻይና ባለሃብቶችን የንግድና ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እያሳደገ ነው

发布:4/30/2026 阅读:3

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የቻይና ባለሃብቶችን የንግድና ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እያሳደገ መሆኑን በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ።

አምባሳደር ቼን ሃይ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ እና ቻይና ታሪካዊና ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት ናቸው።

የኢትዮ-ቻይና ታሪካዊ ግንኙነት የልማት ትብብርን በማጎልበት የሀገራቱን ሁለንተናዊ ግንኙነት እያጠናከረ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

የሀገራቱ የሁለትዮሽ የንግድና ኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ አጋርነት ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ የጋራ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል።

የቻይና ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የሚሰማሩባቸው አዳዲስ የንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎችም ከፍተኛ ዕድገት እያስመዘገቡ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያም የቻይና አልሚ ባለሃብቶችን የኢንቨስትመንት በራስ መተማመን በማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።

ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የፈጠረው የኢትዮጵያ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢም አዳዲስ ዕድሎችን መጠቀም የሚሹ በርካታ የቻይና ባለሀብቶችን እየሳበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የኢትዮ-ቻይና የኢኮኖሚ ትብብርም በግብርና፣ ኢንዱስትሪና የሰው ሃብት ልማት ሶስት ወሳኝ ምሰሶዎችን ማዕከል በማድረግ በስፋት እየተሰራበት መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፈጣን የልማትና የዕድገት አቅጣጫ የሀገራቱን ስትራቴጂክ አጋርነት በማጠናከር ከፍተኛ አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል።

የቻይና ባለሃብቶች የኢትዮጵያ የንግድና የአምራች ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ተሳትፎም የኢኮኖሚ ልማትና ሽግግርን በማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

የሀገራቱ በሰው ሃብት ልማት ትብብር የአዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በክህሎት የበለፀጉ ዜጎችን በማፍራት ወሳኝ ሚና እየተወጣ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በሚቀጥሉት ዓመታትም የሀገራቱን የንግድና ኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ አጋርነት የበለጠ በማጠናከር የሁለትዮሽ ግንኙነትን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራ ጠቅሰዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们