登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

መንግስት ለማዕድን ዘርፍ የሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ 

发布:4/29/2026 阅读:3

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018 (ኢዜአ)፦ መንግስት ለማዕድን ዘርፍ የሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ እንደሚገኝ ምክትል ጠቅላይ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የማዕድን ሀብት በማልማትና ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት በማዋል ረገድ ወደ ተጨባጭ ተግባር መሸጋገሯን አመልክተዋል።


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግራናይት የሚያመርተውን የኦርላመንት (3ኤም) ማርብልና ቴራዞ ማኑፋክቸሪንግ የሥራ እንቅስቃሴ መመልከታቸውን ጠቁመዋል።

ፋብሪካው በክልሉ የሚገኘውን ባለ ብዙ ቀለም የግራናይት ማዕድን በመጠቀም ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ምርት ለገበያ እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ለአካባቢው ማህበረሰብም የሥራ ዕድል ከመፍጠሩ ባሻገር የሀገር ውስጥ ፍላጎትን በመሸፈን የውጭ ምንዛሬን እንደሚያድንም ነው ያብራሩት።


መንግሥት የግሉ ዘርፍ በማዕድን ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፍ የፈጠረው ምቹ ሁኔታ፣ ማበረታቻና ድጋፍ ዛሬ ላይ እንዲህ ያሉ ተጨባጭ ውጤቶችን እያመጣ ነው ብለዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከወርቅ እስከ ግራናይት በተፈጥሮ የታደለ መሆኑን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህንን ፀጋ ለሀገር ብልጽግና ለማዋል የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ይበልጥ እንዲጠናከሩ የፌደራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们