登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

የከተማዋ የአካባቢ ልማት ፕላን ቴክኖሎጂንና ፈጠራን በማስፋፋት የነዋሪዎችን ህይወት ለማሻሻል ያግዛል

发布:4/29/2026 阅读:3

🔇Unmute

አዳማ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የአዳማ ከተማ የአካባቢ ልማት ፕላን ቴክኖሎጂንና ፈጠራን በማስፋፋት የነዋሪዎችን ሕይወት ለማሻሻል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ ሃይሉ ጀልዴ ገለፁ።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከኦሮሚያ ከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የአካባቢ ልማት ፕላን ተፈፃሚነት ዙሪያ በየደረጃው ካሉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ መክሯል።

የአካባቢ ልማት ፕላን (Local Development Plan - LDP) በአንድ በተወሰነ የከተማ ክፍል ወይም መንደር ውስጥ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን፣ የመሬት አጠቃቀም እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታን በዝርዝር የሚመራ የከተማ ፕላን አይነት ነው።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሃይሉ ጀልዴ እንደገለጹት፤ የከተማዋ የአካባቢ ልማት ፕላን ቴክኖሎጂንና ፈጠራን በማስፋፋት የነዋሪዎችን ህይወት ለማሻሻል ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው።

ፕላኑ መሬትን በአግባቡ ለማስተዳደርና ለማልማት ካለው ፋይዳ በተጨማሪ ለከተማ ግብርና፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለቴክኖሎጂ ልማትና ስማርት አዳማ ኢንሼቲቭ ለማሳካት ተጨማሪ አቅም መሆኑንም ተናግረዋል።

የከተማ ፕላኑ የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ እንደሚያግዝም ገልጸዋል።

እንደ ከንቲባው ገለጻ፣ ፕላኑ ከዚህ በፊት የነበሩ የመልካም አስተዳደር እጦት ቅሬታዎችን፣ የመሬት አጠቃቀም ችግሮችና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ያሉ ማነቆዎችን በአግባቡ የፈተሸ ነው።


የኦሮሚያ ከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሸለመ አበበ በበኩላቸው፣ ፕላኑ አዳማ ከተማ ሪጂኦ ከተማ ሆና የተደራጀችበትን ዓላማ የሚያሳካ መሆኑን ተናግረዋል።

የከተማዋን መዋቅራዊ ፕላን በማዘጋጀት ለመስተዳድሩ በማስረከብ ወደ ትግበራ እንደተገባ ገልጸው፣ የአካባቢ ልማት ፕላን መዋቅራዊ ፕላኑን ውጤታማ ለማድረግ ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል።

የአዳማ ከተማን ዕድገትን ለማሳለጥ የተከናወኑ የኮሪደር ልማትና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረተ ልማቶችን መሰረት በማድረግ መዋቅራዊ ፕላኑ መሰራቱንም ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

በክልሉ የአዳማ፣ የቢሾፍቱና የሻሸመኔ ከተሞች በሪጂኦ ማዕቀፍ ውስጥ ሆነው ወደ ልማት ሥራ መግባታቸውን አንስተው የጂማ፣ ማያ፣ ሮቤ እና ነቀምት ከተሞች መዋቅራዊና የአካባቢ ልማት ፕላኖችም እየተዘጋጁ መሆኑን ጠቅሰዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们