登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

发布:4/24/2026 阅读:1

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል የሚያደርጉ ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ከንቲባ አዳነች ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ 11ኛውን ከተማ አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ በይፋ ከፍተዋል።


“በሳይንስና ፈጠራ የተካነ ትውልድ ለተምሳሌታዊ ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የሚደረገው አውደ ርዕይ ዛሬ እና ነገ ክፍት ሆኖ ይቆያል።

ከንቲባዋ አውደ ርዕዩን በከፈቱበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ መድረኩ የከተማዋን የፈጠራ ጉዞ አንድ ደረጃ የሚያራምድ መሆኑን ገልጸዋል።

የዛሬው የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ዋነኛ ዓላማ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን ትምህርት በተግባር የሚያሳዩበት መድረክ መፍጠር እንደሆነ አመልክተዋል።

አያይዘውም ተማሪዎች የውስጥ ተሰጥዖዋቸውን የሚገልጹበት፣ ለሰሯቸው የፈጠራ ስራዎች ዕውቅናና ማበረታቻ የሚያገኙበት እንዲሁም እርስ በእርስ በትብብር የመስራት ልምድ የሚለዋወጡበት ትልቅ መድረክ ነው ብለዋል።


እውነተኛ እውቀት ችግሮችን ደጋግሞ ማውራት ሳይሆን ለችግሮች መፍትሄ ማፍለቅና ችግርን ወደ ድል መቀየር መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባ አዳነች፣ አዲስ አበባን የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

አሁን ላይ የተጀመሩ ስራዎች ውጤት በተጨባጭ መታየት የጀመረበት ወቅት ላይ መደረሱን ገልጸው፣ ይህ ውጤታማ ጅምር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ዛሬ የፈጠራ ስራቸውን ያቀረቡ ተማሪዎችና መምህራን ላይ ትልቅ ተስፋ እንዳላቸው የገለጹት ከንቲባዋ፣ እነዚህ የፈጠራ ስራዎች አድገውና በልጽገው ለከተማዋ፣ለሀገር ብሎም ለዓለም የሚተርፍ በረከት እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们