登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በሳይንስና ፈጠራ የተካነ ትውልድ የሀገርን ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

发布:4/24/2026 阅读:1

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በሳይንስና ፈጠራ የበለፀገ ትውልድ መገንባት ለሀገር ብልጽግና እና ሁለንተናዊ እድገት መሰረት በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ “በሳይንስና ፈጠራ የተካነ ትውልድ ለተምሳሌታዊ ሀገር” በሚል መሪ ሐሳብ ያዘጋጀው 11ኛው የሳይንስና የፈጠራ ሥራ ዐውደ-ርዕይ በአራዳ ፓርክ እየተካሄደ ይገኛል።


በዚህ መድረክ ላይ በርካታ ተማሪዎችና መምህራን የፈጠራ ሥራዎቻቸውን ለዕይታ አቅርበዋል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዐውደ-ርዕዩን በጎበኙበት ወቅት እንደተናገሩት፤ መድረኩ ተማሪዎችና መምህራን የፈጠራ ሥራዎቻቸውን የሚያስተዋውቁበትና እርስበርስ የፈጠራ ሐሳባቸውን የሚለዋወጡበት ወሳኝ ድልድይ ነው።


በዐውደ-ርዕዩ የቀረቡት የፈጠራ ውጤቶች ከተማዋን ወደ ስማርት ሲቲ ለመቀየር እየተደረገ ላለው ጥረት ትልቅ ተስፋ የሚሰጥና የምሥራች መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ማንኛውም የፈጠራ ሥራ ውጤት በትንሽ ጅማሮ የሚነሳ መሆኑን ጠቅሰው፤ መንግሥት እነዚህን የፈጠራ ሥራዎች በፋይናንስና በሙያ በመደገፍ ወደ ላቀ ደረጃ እንዲሸጋገሩ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።


በአሁኑ ወቅት በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች በሳይንስና በቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም አክለዋል።


ዐውደ-ርዕዩ የፈጠራ ውጤቶችን ወደ ተግባር በመቀየር የሀገርን ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጉዞ እንደሚያፋጥን ታምኖበታል ነው ያሉት።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) እንደገለጹት መድረኩ ተማሪዎች ዕውቀት የሚያገኙበት ብቻ ሳይሆን፤ የጥበብ ባለቤት መሆናቸውን በተግባር የሚያሳዩበት ነው።

ባለፉት ዓመታት ጥቂት ተማሪዎች ይሳተፉበት የነበረው የምርምርና ፈጠራ ሥራ ዛሬ የብዙዎች ባህልና ጉጉት መሆኑን መድረኩ ማረጋገጡንም ጠቁመዋል።

ይህ የፈጠራ እድገት በከተማዋ በስፋት ከሚከናወኑ መሠረተ-ሰፊ የልማት ሥራዎችና ፕሮጀክቶች ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑንም አብራርተዋል።


የቅድመ-1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በዓይነትና በጥራት መስፋፋታቸው ሕፃናት በራስ የመተማመን ስሜት ትምህርታቸውን እንዲጀምሩና ለሳይንስ ሥራዎች ጠንካራ መሠረት እንዲጥሉ እያደረገ ነው ብለዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们