登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

发布:4/24/2026 阅读:1

🔇Unmute

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ።

ኃላፊው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የሚመረተው የቡና ምርት ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለገበያ እየቀረበ ነው፤ አቅርቦቱም በየዓመቱ እያደገ መጥቷል።


ለአርሶ አደሩ በየጊዜው የሚደረገው ድጋፍ፣ ክትትልና ሥልጠና የቡና ጥራትን በተሻለ ሁኔታ መጠበቅ እንዳስቻለም ገልጸዋል።

ዘንድሮ 300 ሺህ ቶን የቡና ምርት መሰብሰቡን ገልጸው፤ ከዚህ ውስጥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለሀገር ውስጥና ለውጪ ገበያ ማቅረብ ተችሏል ብለዋል።



ጥራት ያለው ቡናን ለገበያ በማቅረብ ሂደት ውስጥ መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ድርሻ የላቀ መሆኑንም አመላክተዋል።


የጅማ ዞን የኅብረት ሥራ ማኅበራት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ድማሙ ንጋቱ በበኩላቸው፤ በዞኑ 1 ሺህ 300 መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማኅበራትና 4 ዩኒየኖች እንደሚገኙ ገልጸዋል።


በቡና ምርት ላይ የተሰማሩ ዩኒየኖች በቡና ጥራትና አቅርቦት ላይ በትኩረት እየሠሩ መሆኑን ተናግረዋል።


ዘንድሮ 4 ሺህ 800 ቶን የታጠበና ስፔሻሊቲ ቡና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የዕቅዱን 60 በመቶ ማቅረብ መቻሉን አረጋግጠዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们