登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

ኤክስፖዎች የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅምና የእርስበርስ ትስስር እያጠናከሩ ነው

发布:4/24/2026 阅读:1

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚዘጋጁ ኤክስፖዎች የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅምና የእርስበርስ ትስስር በማጠናከር ተወዳዳሪነትን ለማላቅ መደላድል እየፈጠሩ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ።

ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልጽግ በሚል መሪ ሐሳብ በድሬዳዋ የተዘጋጀ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ኤክስፖ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተከፍቷል።


የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት፤ ኤክስፖዎች የአምራች ኢንዱስትሪዎች የምርት ጥራትና ደረጃን በማሟላት ረገድ የደረሱበትን ከፍታ ለማሳየትና ለሚስተዋሉ ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እያገዙ መሆኑን ተናግረዋል።


በተጨማሪም የእርስበርስ ትስስርን፣ መመጋገብንና ውድድርን በማጠናከር ሀገራዊ ትልምን ከዳር ለማድረስ ምቹ መደላድል እየፈጠሩ መሆኑን አስረድተዋል።

ከሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ሀገር አቀፍ ኤክስፖ እንደሚዘጋጅም ጠቁመዋል።

በኤክስፖው ላይ ምርታቸውን ያቀረቡ የአምራች ኢንዱስትሪ ተወካዮች በበኩላቸው፤ የግብዓት ልውውጥና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ኤክስፖዎች መዘጋጀታቸው ለአምራች ኢንዱስትሪው ወሳኝ አበርክቶ እንዳላቸው ገልጸዋል።


ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተደረገላቸው ድጋፍ ወደ ማምረት የተሸጋገሩ አዳዲስ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们