登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ እድገቱ የሚያበረክተውን ሚና ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቷል

发布:4/24/2026 阅读:1

🔇Unmute

አርባምንጭ፤ ሚያዝያ 15/2018 (ኢዜአ)፡- አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ እድገቱ የሚያበረክተውን ሚና ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሠ መሥተዳድርና የሥራና ክኅሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሠ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።

ክልል አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር በአርባ ምንጭ ከተማ የተከፈተ ሲሆን፤ የፓናል ውይይትም ተካሂዷል።


አበባየሁ ታደሠ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ አምራች ኢንዱስትሪው ተኪ ምርት ከማምረት አንፃር ያለውን ሚና ለማጉላት በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚ እድገቱ የሚያበረክተውን ሚና ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን አረጋግጠዋል።


የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴዔታ ታረቀኝ ቡሉልታ በበኩላቸው፤ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሙሉ ዐቅማቸው እንዲያመርቱ የፋይናንስና የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የገበያ ችግሮችን ለመፍታት ሁለንተናዊ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

የኢንዱስትሪ ልማትን በማፋጠን ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ በመገንባት ጠንካራ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለመፍጠር በቅንጅት እየተሠራ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ሰለሞን ናቸው።


ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከ3 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 30 ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቅሰው፤ ለ27 ሺህ 817 ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውንም አስረድተዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们