登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

ኢትዮጵያ ለአካባቢ ጥበቃ ሥራ የላቀ ውጤታማነት አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን እንደ ወሳኝ ግብዓት እየተጠቀመች ትገኛለች

发布:4/24/2026 阅读:1

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ እያከናወነች ያለችውን ውጤታማ ሥራ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን እንደ ወሳኝ ግብዓት እየተጠቀመች መሆኑን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ገለጹ።

ኢንስቲትዩቱ ከኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው "የአካባቢ ብክለት ዲጂታል ሪፖርት ማድረጊያ ሥርዓት" በይፋ ስራ አስጀምሯል።


ይህ አዲስ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የአካባቢ ጥበቃና የብክለት ቁጥጥር ሥራን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ የዳታ ትንተና በማከናወን ለማዘመን ያለመ ነው።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ተቋሙ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ "ኤ.አይ ለሁሉም" በሚል መርህ ሀገራዊ የልማት ግቦችን የሚደግፉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን እያመረተ ይገኛል።

ይህ ዛሬ ይፋ የሆነው መተግበሪያም ህብረተሰቡ የብክለት ጥቆማዎችን በቀላሉ እንዲያደርስና በፈጣን የዳታ ትንተና አማካኝነት ተገቢው ምላሽ እንዲሰጥ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።

የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍስሃጽዮን ፤ መንግሥት የአሁኑንና የቀጣዩን ትውልድ ተጠቃሚነት ታሳቢ ባደረገ የኢኮኖሚ ልማት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።


ዛሬ ይፋ የሆነው ዲጂታል መተግበሪያ መንግሥት በዘርፉ የሚወስዳቸውን የፖሊሲ ማሻሻያዎችና ፈጣን ምላሾች በዳታ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ለማድረግ እንደ ግብዓት የሚያገለግል መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሌሊሴ ነሜ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ መተግበሪያው በተለይ በከተሞች የተገነቡ የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ እና የጽዳት ሥራዎችን በዘላቂነት ለመጠበቅ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።


ቴክኖሎጂው ተቋማቸው በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲወስንና የብክለት ምንጮችን በቅርበት መቆጣጠር የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥርም ተናግረዋል።

በመሆኑም ፅዱ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ህብረተሰቡ በንቃት በመሳተፍ ጥቆማዎችን በመተግበሪያው በኩል እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።

ይህ የዲጂታል ሪፖርት ማድረጊያ መተግበርያ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራና በከተሞች ውበት ላይ የጀመረቻቸውን ስኬታማ ሥራዎች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ የተሻለ የአየር ንብረት ለመፍጠር ለሚደረገው ጉዞ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተገልጿል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们