登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በድሬዳዋ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 84 የተዘጉና በግንባታ ላይ የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል

发布:4/23/2026 阅读:1

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በድሬዳዋ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 84 የተዘጉና በግንባታ ላይ የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።

በአስተዳደሩ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ እየተመዘገቡ የሚገኙ ውጤቶችን የሚያሳይ "ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የኢንዱስትሪ ኤክስፖ ነገ ይጀመራል።

ኤክስፖውን አስመልክተው የአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኡስማን አህመድ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

አቶ ኡስማን እንደገለጹት፤ ባለፉት አራት ዓመታት በተካሄደው እና ዘንድሮም በቀጠለው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ተዘግተውና በግንባታ ላይ የነበሩ 84 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት ተሸጋግረዋል።

በንቅናቄው በተደረጉ ልዩ ድጋፍ እና ክትትሎች የመካከለኛ እና ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የፋይናንስ፣ የመሬት፣ የመሠረተ ልማት፣ የኤሌክትሪክ እና የሌሎች አገልግሎት ጥያቄዎች በተቀናጀ መልኩ መፈታታቸውን አንስተዋል።

ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡት እነዚሁ ኢንዱስትሪዎች 87 ዓይነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በራስ አቅም በማምረት የውጭ ምንዛሬን እያስቀሩ ይገኛሉ ብለዋል።

ከ17 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠራቸውንም አንስተዋል።

ለአራተኛ ጊዜ የተዘጋጀው እና ነገ በይፋ በሚጀመረው ኤክስፖው ላይ 50 አምራች ኢንዱስትሪዎች የተለያዩ ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ የገበያ፣ የግብአትና የእርስ በርስ መመጋገብ እና ትስስር እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል።

ለአንድ ሳምንት በሚዘልቀው ኤክስፖው ላይ የፌደራልና የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ የዘርፉ አመራሮች እንደሚሳተፉም ይጠበቃል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们