登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

የቅርስ ጥበቃ እና ልማት ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው ሚና አድጓል

发布:4/22/2026 阅读:1

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ለቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ዘርፉ ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው ድርሻ ማደጉን የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ገለጹ።


3ኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ የኢትዮጵያ ቅርስ ምርምር በዲጂታል ዘመን በሚል መሪ ሐሳብ መካሄድ ጀምሯል።

ሚኒስትር ዴዔታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የለውጡ መንግሥት በቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራን በተመለከተ ልዩ ትኩረት በመስጠቱ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል።


ቅርሶች የውጭ ምንዛሪን በማስገኘት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር እንዲሁም ለአርኪዎሎጂስቶችና ለታሪክ ተመራማሪዎች የማይነጥፍ የመረጃ ምንጭ ሆነው እያገለገሉ እንደሚገኙ አብራርተዋል።

ቅርሶች ተጠብቀው ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ የማድረግ፣ የቅርስ አያያዝንና አጠቃቀምን የማዘመን ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


የቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራው ዲጂታላይዝ እየተደረገ ነው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረ/ፕ) ናቸው።


ጉባዔው በቅርስ ልማት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን መርምሮ መፍትሔ ለመስጠትና አዳዲስ ዕውቀቶችን ለመለዋወጥ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们