🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ከ81 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው የአፈር ለምነት ማሻሻያ ባለሙያ አምሳሉ አድማስ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የአፈር ለምነትን በዘላቂነት ለማሻሻል ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በበጀት ዓመቱ ከ76 ነጥብ 5 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ81 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ከተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ግማሽ ያህሉን በ1 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ በመበተን ከአፈር ጋር የማዋሃድ ሥራ መሰራቱንና በቀሪው ማዳበሪያም ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ ሳይንሳዊ አሰራሩን ተከትሎ በጥራት ከተዘጋጀ የአፈር ስነ ህይወታዊ ዘዴን በማሻሻል ለምነቱን በቀላሉ ለመመለስና ምርታማነትን ለማሳደገ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንምአስረድተዋል።
ባለፈው ዓመት በክልሉ ከ71 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኩብ በላይ ኮምፖስት በማዘጋጀት ጥቅም ላይ መዋሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
微信扫一扫 立即联系我们