登录以查看您的控制台资源

新闻通稿 SEO营销 媒体监测

联系我们

በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው

发布:5/12/2026 阅读:1

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተገኘ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ።


ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ ሎካ አባያና ደራራ ወረዳዎች በበልግ ወቅት በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን የበቆሎ ማሳ በመስክ ተመልክተዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ገበያን የሚያረጋጋ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተከናወኑ ባሉ ተግባራት ውጤት እየተገኘ ነው።


በዚህም በበልግ ወቅት ፆም የሚያድር መሬት እንዳይኖር በማድረግና ግብዓቶችን በወቅቱ በማቅረብ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ስራ የምርት ቁመናው ተስፋ ሰጪ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በበልጉ ያለውን አመቺ የዝናብ ስርጭት እንዲሁም የቴክኖሎጂ አቅርቦት በመጠቀም የተሻለ ምርት ለማግኘት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት አሁን ላይ ለማሳ እንክብካቤ ስራ ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል።


በክልሉ ያለውን የእርሻ አቅም አሟጦ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና በምግብ ራስን የመቻል ግብን ለማሳካት የሚደረጉ ጥረቶች ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመው ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።


በበልግ ወቅት በክልሉ በሰብል የሚለማ የመሬት መጠን እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ አብዛኛው መሬት በምርጥ ዘር መሸፈኑን ተናግረዋል።


የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ በበልግ እርሻ ከ152 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ዋና ዋና ሰብሎች እንዲሁም በስራስርና አትክልቶች መሸፈኑን ተናግረዋል።


አጠቃላይ ከለማው መሬትም ከ24 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።


በልማቱ እየተሳተፉ ካሉ መካከል በሎካ አባያ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ጽጌ ኩማ እንደገለጹት የአካባቢው 80 አርሶ አደሮች ከ75 ሄክታር በላይ ኩታ ገጠም መሬት ላይ በቆሎ እያለሙ መሆናቸውንና የማሳ እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።


ሌላው በዳራራ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ዳዊት ብንኦ 40 ሆነው በኩታገጠም በቆሎ እያለሙ መሆናቸውን ጠቁመው ምርቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና በጋራ መስራታቸው ውጤታማ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።

传播你的梦想,是我的使命

精准触达,高效发声,让每一次发布都有回响,把专业的事,交给专业的人,助你专注核心,我们搞定传播。

微信扫一扫 立即联系我们